Friday, September 28, 2012

የትችት ባሕላችንን ብንተቸውስ?




ከግሪክ፣ የኤሶጵ ተረቶች አንዱ እንዲህ ይተረካል፡፡ አንድ ሰውዬ እና ልጁ፣ አህያቸውን አስከትለው ወደገበያ ሲሄዱ የተመለከታቸው የአገሩ ሰው፣ ‹‹እናንት ሞኞች፣ አህያው እኮ የተፈጠረው ሊጋለብ ነው›› ይላቸዋል፡፡ አባት ልጁን አህያው ላይ ጭኖ ትንሽ እንደተጓዙ የሆኑ ሰዎች ይመለከቱ እና ‹‹ምን ዓይነት የተረገመ ልጅ ቢሆን ነው አባቱን በእግሩ እያስኬደ እሱ የሚጋልበው?›› አሉ፡፡ አባት ልጁን አስወርዶ ራሱ መጋለብ ቀጠለ፤ ጥቂትም ሳይጓዙ ግን ‹‹ምን ዓይነት ክፉ አባት ነው ልጁን በእግሩ እያስኳተነ እሱ አህያ የሚጋልብ?›› ብለው የሚተቹ ሰዎች አለፉ፡፡ ግራ የተጋባው አባት ልጁን ከኋላው ጭኖ አህያውን ለሁለት ይጋልቡት ጀመር፡፡ ይህንን የተመለከቱ ሰዎች ‹‹ምን ዓይነት ጭካኔ ነው፣ አንድ አህያ ለሁለት የሚያስጋልባችሁ?›› አሏቸው፡፡ ግራ የተጋቡት አባትና ልጅ በመጨረሻ አህያውን ለሁለት ተሸክመውት ገበያ በመግባት የገበያተኛው መሳለቂያ ለመሆን በቅተዋል፡፡

የተረቱ ሞራል፣ ሁሉንም ማስደሰት እንደማይቻል ነው፡፡ ይሁን እንጂ ሁሉንም የሚያስማማ መፍትሄ ባይገኝም ቅሉ ለትችቱ መፍትሄ ለመስጠት ባደረጉት መፍጨርጨር አባት እና ልጅም በፈረቃ ጋልበዋል፣ አህያውም አርፏል፡፡ የሚቀበሉትን ትችት ማወቅ እና አለማወቅ፣ ብሎም ለትችቱ ሁነኛውን መፍትሄ መፍጠር የተተቺው ድርሻ ቢሆንም ‹ትችት› ግን የማይቀር እና ሊቀር የማይገባው ነው፡፡

አሁን የራሳችንን ትችት ባሕል ወደመተቸት እናልፋለን፤ የትችት ባሕላችንን ከመተቸታችን በፊት ግን ለቃሉ ትርጉም በማበጀት ብንጀምር መልካም ነው፡፡ ‹ትችት› የሚለው ቃል ከመነሻው አሉታዊነት እንዳለበት የሚከራከሩ አሉ፡፡ እነዚህ ተከራካሪዎች ‹ሂስ› የሚለው ቃል የተሻለ አስማሚ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ በሁለቱ ቃላት መካከል ያለውን ልዩነት ማስታረቅ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ስላልሆነ - ሳይስማሙ እንዲኖሩ እንተዋቸውና ‹ትችት› በዚህ ጽሑፍ ውስጥ እንዲኖረው ስለሚፈለገው ትርጉም እንነጋገር፡፡

‹ትችት› በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ‹‹በሆነ ርዕሰ ጉዳይ፣ ሐሳብ፣ ፍልስፍና፣ ድርጊት ወይም የሥራ ውጤት ላይ የሚሰነዘር፣ በምክንያት ላይ የተመሰረተ የተቃርኖ ወይም የነቀፌታ አስተያየት ነው፡፡››

በአገራችን ለትችት የተነወሩ (አይነኬ) በርካታ ጉዳዮች አሉ፡፡ ከነዚህ ጉዳዮች መካከል ለጠቅላላ የትችት ባሕላችን ጉብጠት ምሳሌ ይሆናሉ በሚል በጥንቃቄ የመረጥኳቸውን ጉዳዮች እያነሳሁ ለማቅናት እደረድራለሁ፡፡ ትችቴ ያልተስማማው የመልስ ምት ቢጽፍ በዞን ዘጠኝ ጦማር ላይ ለማስፈር ከወዲሁ ቃል እገባለሁ፡፡

Monday, September 24, 2012

ሰለጠቅላይ ሚንስቴር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፦ ያልተባሉና ያልተነገሩ


በቀድሞ ተማሪያቸው
I.      መግቢያ፡-

የጠቅላይ ሚንስተር አቶ መለስ ዜናዊ ድንገተኛ ሞት ተከትሎ የአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ያልተጠበቀና ያልታሰበ ወደስልጣን መምጣት ብዙዎችን ያስገረመ ጉዳይ ሲሆን ይህንንም ተከትሎ የዚች ሃገር  ጉዳይ  ያገባኛል ያሉ ብዙ ግለሰቦች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማሀበራት እና ሌሎችም የሳቸው ሹመት ለሃገሪቱ ጥሩ አጋጣሚ ሊሆን እንደሚችልና ምናልባትም ፈጣሪ ለዚች ሃገር ለውጥ ያስቀመጣቸው ሊሆኑ ሁሉ እንደሚችሉ ተስፋ አድርገውባቸዋል፡፡ እኔም ከነዚህ ወገኖች አንዱ ነኝ፡፡

ይቅርታ የሚገባው የኢትዮጵያ ሕዝብ!


እነሆ ኢትዮጵያ አዲሱን ጠቅላይ ሚኒስትሯን አግኝታለች፡፡ አንድ መሪ ሲሞት ያለምንም ጦርነት እና ገሀድ የወጣ ሽኩቻ ምክትሉ ሲታካው በአገራችን የታየው ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን መካድ አይቻልም፡፡ ይህ ግን የሚኩራሩበት ችሮታ ሳይሆን ሊታዘዙለት የሚገባ  ሕገ መንግስታዊ መርሕ ነው፡፡ መጪው መሪ ያለፈውን ዘመን ትንሽዋን ስኬት የማክበጃ ፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ባሕል ቀጭተው ወደ ተግባራዊ ለውጦች በመግባት ለውጡ የእውነት መሆኑን ለማሳየት ጊዜው አሁን ነው፡፡ የሆነ ሆኖ የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓላማ ይህ አይደለም፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር ሕመም እና ሞት ተከትሎ የነበሩትን ዘገባዎች ይመለከታል፡፡

አቶ መለስ ዜናዊ መታመማቸው በወሬ ደረጃ መናፈስ ከጀመረ በኋላ ሚዲያዎቻችን በተቃራኒ ጽንፎች ሲወዘወዙ ከርመዋል፡፡ በመጀመሪያ ላይ ስለጉዳዩ የተጠየቁት የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮው አቶ ሽመልስ ከማል፥ ‹‹ወሬው የኢሳት ነው፤›› ብለው አጣጥለውት (ወይም ዋሽተው) ነበር፡፡ እኚህ የመንግስት ተጠሪ “የነበሩ” ሰው፣ ሕዝብ የመንግስት ጉዳዮችን የማወቅ ሕገመንግስታዊ መብቱን በመግፈፍ፣ አውቀው - በማን አለብኝነት፣ አሊያም በስህተት የተናገሩትን ተናግረዋል፤ ነገር ግን በጥቂት ቀናት ውስጥ አለቃቸው አቶ በረከት ስምኦን ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀለል ያለ ሕመም›› እንደገጠማቸው ተናግረዋል፡፡

Thursday, September 20, 2012

ቤተመንግስቱ ኃይለማርያምን የሚያሰራ ይሆን?




ነብዩ ኃይሉ

ላለፉት 21 አመታት የምኒሊክ ቤተመንግስት ለአንድና ለሁለት ቀን ግፋ ሲልም ለአንድ ሳምንት ካልሆነ ጌታውን አጥቷቸው አያውቅም፡፡ አቶ መለስ በግንቦት ወር በቡድን ስምንት ጉባኤ ከተካፈሉ በኋላ ግን ማንንም አምነው የማይርቁትን ቤተመንግስት በህመም ምክንያት ትተው ብራስልስ ከረሙ፡፡ ህመማቸው እና አማልክቱ ጨክነውም ዳግም ወደ ምኒሊክ ቤተ መንግስት በቁማቸው ሳይመለሱ ቀሩ፡፡ እናም ቤተመንግስቱ ላለፉት ሦስት ወራት ኦና ሆኗል፡፡

Monday, September 17, 2012

እኛና ሶማሊያ




ከአምስት መቶ ዓመታት በፊት አሁን ሶማሊያ ተብላ የምትጠራውን ሀገር አብዛኛውን ግዛት ያስተዳድር የነበረው አሕመድ ግራኝ በሰሜን የሚያዋስኑት ባብዛኛው ክርስትያንያዊ ከሆኑ አስተዳደር ግዛቶች ላይ ያካሄደው አስከፊ ወረራ አሁን ኢትዮጵያ ተብላ በምትጠራው አገራችንና በጎረቤት አገር ሶማሊያ መካከል ጊዜ እየጠበቀ ለሚያገረሸው ጦር መማዘዝ እና ቁርሾ የመጀመርያው አድርገው ይወስዱታል አንዳንድ ተንታኞች፡፡ 

ሁለቱ አገሮች ዘመናዊ በሆነ ማዕከላዊ መንግስት መተዳደር ከጀመሩበትና ሶማሊያ ከቀኝ አገዛዝ ነፃ ከወጣችበት ጊዜ አንስቶ ቢያንስ ሁለት ጊዜ በይፋ ጦር ተማዘዋል፡፡ ከቀዝቃዛው ጦርነት ማብቃት ጋር አብሮ ሶማሊያ ማዕከላዊ መንግስት ካጣች በኋላ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስት ለደህንነቴ ስጋት እየፈጠሩ ነው ያላቸው ታጣቂዎች ላይ በተለያየ ወቅት ጥቃት ሲፈጽም ቆይቷል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ የኢትዮጵያ ጦር ጥቃቱን የሚፈፅመው ድንበር አካባቢዎች ላይ ወይንም ድንበር አልፎ ከገባም ጥቃቱን ፈፅሞ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ነበር ለቆ የሚወጣው፡፡ ጥቅሙን የሚያስጠብቁ የጎሳ ሪዎችንም ያስታጥቃል በሚል የኢትዮጵያ መንግስትን ክስ የሚያቀርቡበትም ጥቂት አልነበሩም፡፡

እንደ ኢትዮጵያውያን ዘመን አቆጣጠር በሰኔ ወር 1998 ዓ.ም የእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ሕብረት በሚል እራሱን የሚጠራ ቡድን የሶማሊያን ዋና ከተማ ሞቃዲሹንና አብዛኛውን የአገሪቱን ደቡባዊ ግዛቶች ተቆጣጠረ፡፡ እንደ ብዙዎች ዕይታ በዚያድ ባሬ የሚመራው መንግስት ወድቆ አገሪቷ መንግስት አልባ ከሆነች በኋላ ሶማሊያ ለመጀመሪያ ጊዜ አንፃራዊ ሰላም እና ሰፊ ግዛት የሚያስተዳድር መንግስት ያገኘችው ሕብረቱ ሞቃዲሹን በቁጥጥር ስር ሲያውል ነበር፡፡

Sunday, September 16, 2012

የሳምንቱ ጋዜጣና መጽሔቶች ከሰኞ እስከ ሰኞ




ሰንደቅ ጋዜጣ

ሰንደቅ ጋዜጣ በዚህ ሳምንት አትሙ 2004 . ጉልህ ክስተቶች የሚል የፌት ገጽ ይዞ ወጥቶዋል፡፡የአመቱ ዋና ዋና ክስተቶች ናቸው የተባሉት መካከልም የደርግ ባለስልጣናት መፈታት፣ኢትዮጵያ ለአሜሪካ ሰው አልባ ጄቶች ማኮብኮቢያ መፍቀዱዋ፣አወዛጋቢው 70/30 የበጎድራጎት ድርጅቶች ህግ የአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ መዘጋት እና የዳቦ ዋጋ ጭማሪ፣የአበራሽ ሃይላይ ጉዳይ እና የግብረሰዶማዊያኑ ስብሰባ በኢትዮጵያ ይገኙበታል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን በእንግድነት ይዞ የመጣው ሰንደቅ ዳንኤልየሚያስጨንቀኝ ቀጣዩ ፓትሪያርክ ሳይሆን ቀጣይዋ ቤተክርስቲያን ናትማለቱን ጠቅሶዋል፡፡

አዲስጉዳይ መጽሔት

ባለፈው ሳምንት ለገበያ መብቃት ያልቻለችው አዲስ ጉዳይ መጽሔት በበኩልዋ የአመቱን አነጋጋሪ ጉዳይ ሞት በማድረግ በአመቱ በሞት የተለዩ ታላላቅ እና ታዋቂ ሰዎችን ይዛ ወጥታለች፡፡በዋና ዋና አምዶቹም
         የአዲስ ዓመት ገበያ
         ሞት የአመቱ አነጋጋሪ ጉዳይ
         መለስ ዜናዊ የአመቱ አብይ ጉዳይ
         2004 የኢትዮጵያ ፖለቲካ የተጠበቀው የቀረበት ያልተጠበቀው የመጣበት
         2004 ያልተቋጨው የህዝብ ብሶት (ከሊዝ አዋጅ እስከ ኑሮ ውድነት፣የሙስሊሙ ህብረተሰብ የመብት ጥያቄ) ሲሆኑ የተለመዱት ቋሚ አምደኞችም የተለያዩ ጽሁፎቻቸውን ይዘው ወጥዋል፡፡

አዲስ አድማስ

አዲስ አድማስ በቅዳሜ እትሙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ተቀዛዝዋል በሚል ዜና የፊት ገጽ ዜና ይዞ የወጣ ሲሆን ዶር ነጋሶ ጊዳዳን በፓርቲው ጋዜጣ ፍኖተ ነጻነት መታገድ እና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ አናግሮዋቸዋል፡፡አድማስ በተጨማሪም በፊት ገጽ ዜናው እና አህመዲን ጀማል /ቤቱን ይቅርታ ጠየቁ የሚል ዜና ይዞ ወጥቷል፡፡

የሙስሊም ማህበረሰብ ችግር መፍትሔ አፈላላጊ በተሰኘው ኮሚቴ ውስጥ ከሚገኙ 17 አባላት መካከል ስምንቱ በረመዳን ወቅት ከተከሰተው ግጭት ጋር ተያይዞ መታሰራቸውና መከሰሳቸው የሚታወቅ ሲሆን፤ ተከሳሾቹ ለእስልምና ጉዳዮች /ቤት የይቅርታ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ምንጮች ጠቆሙ፡፡ የኮሚቴው አባላት ከምክር ቤቱ ጋር በነበራቸው ግጭት፤ የምክር ቤት ምርጫ ለረዥም ጊዜ ተቋርጦ መቆየቱን በመጥቀስ ምርጫ እንዲካሄድ መጠየቃቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ምርጫው እንደሚካሄድ ከተወሰነ በኋላ ምርጫ የት ይካሄድ በሚለው ጥያቄ አለመግባባት መፈጠሩ ይታወቃል፡፡ ውዝግቡ መፍትሄ ሳያገኝ በረመዳን ወቅት ወደ ግጭት እንደተሸጋገረ የሚታወስ ሲሆን፤ ከኮሚቴው አባላት መካከል ስምንቱ ታስረው ክስ እንደቀረበባቸው ታውቋል፡፡ ተከሳሾቹ የሠራነው ስራ ስህተት በመሆኑ እንደገና በመወያየት ወደተሻለና አዲስ አሠራር እንድንመጣ እንፈልጋለን በማለት ለም/ቤቱ ደብዳቤ እንዳስገቡ የገለፁት ምንጮች፤ የተከሰሱበት ክስ ቀርቶ በይቅርታ ሊፈቱ ይችላሉ በማለት ግምታቸውን ገልፀዋል፡፡ የመጽሔት አዘጋጅ የሆነውን አህመዲን ጀማልን ጨምሮ በእስር በሚገኙት ስምንት አባላት ፊርማ ደብዳቤው ለምክር ቤቱ እንደደረሰም ምንጮቹ ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል በቀረበባቸው ክስ /ቤት ለጥቅምት 2 ቀን 2005 . ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ብሏል አድማስ በዘገባው